የግልግል ዳኝነት እና የዕርቅ አሰራርን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር—-/2011
የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚያዊ፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የመሳሰሉት አለመግባባቶችን በግልግል ዳኝነትና በዕርቅ መፍታት
አስፈላጊ በመሆኑ ፤
የፍርድ ቤቶችን ጫና፣ የጊዜ መጓተት፣ ተገቢ ያልሆነ ወጪ ለማስቀረት እና የተከራካሪ ወገኖችን ሕጋዊ መብትና ጥቅም ለመጠበቅ
አለመግባባቶችን በአማራጭ የዳኝነት ሥርዓት መፍታት አስፈላጊ በመሆኑ፤
የግልግል ዳኝነትና ዕርቅ ኢትዮጵያ ተቀብላ ያጸደቀቻውንና ዓለም ዓቀፍ የግልግል ዳኝነት ስምምነቶች ተግባራዊ ለማድረግ
እንዲሁም ለነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ማደግ አስተዋጽዖ የሚያደርግ በመሆኑ፤
በውጭ ሀገር ለተሰጡ የግልግል ዳኝነት ፍርዶች እውቅና መስጠት እና ማስፈፀም አስፈላጊ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) እና (6) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
DOWNLOAD
የግልግል ዳኝነት እና የዕርቅ አሰራርን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር Draft
Categories: Draft Laws, Draft Proclamations
Its’ an interesting..!